Cannabis Ruderalis

Content deleted Content added
MfactDr (talk | contribs)
Undid revision 1012995285 by Davethequarit (talk) unsourced
Tag: Undo
213.55.79.194 (talk)
No edit summary
Tags: Reverted non-English content
Line 32: Line 32:
* Ambaw washa
* Ambaw washa


== ታሪክ==
* ቋሪት በምዕራብ ጎጃም ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች አንደኛው ነው፡፡ ወደ ቋሪት ለመዝለቅ ሁለት መንገዶችን መጠቀም ግድ ይላል፡፡ ይኸውም በጂጋ ከተማ በኩል በመኪና ወደ ላይ 45 ኪሎ ሜትር በመጓዝ፣ ወደ ወረዳው ከተማ ገበዘ ማርያም ለመድረስ ይቻላል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በሞጣ ባሕርዳር መንገድ ከይልማና ዴንሳ ወረዳ ከተማ ከአዴት በመኪና ወይንም በእግር ተጉዞ ወደ ገበዘ ማርያም ለመግባት ይቻላል፡፡ በተለይ ግን ከአዴት እስከ ብር አዳማና ቋሪት ከተማ ወይም ከጅጋ እስከ ገበዘ ማርያም ያለው መንገድ በእጅጉ አስቸጋሪ ነው። በእነዚያ መንገዶች የሚጓዝ መንገደኛ መኪናው እየነጠረ፣ ወገቡ እየተሰበረ ለመሄድ ይገደዳል። መኪናም እንደ ልብ ስለማይገኝ ነጋዴዎች ሸቀጦቻቸውን ከቦታ ወደ ቦታ የሚያመላልሱትና የሚገበያዩት በአጋሰ5ስ ላይ በመጫን ነው፡፡ በቋሪት አካባቢ ወይበይ፣ ብር አዳማና ጨጎዴ ሐና የተባሉ ቦታዎችን ስም በተደጋጋሚ መስማት የተለመደ ነው፡፡ የቋሪት ከተማ ገበዘ ማርያም በሰንሰለታማ ተራራዎች ሥር ትገኛለች፡፡ ቀደም ሲል ከተማዋ ዳቢ ትባል ነበር፡፡ የቋሪት የመጀመሪያ ገበያ (እናንጊያ ሚካኤል አጠገብ የተመሠረተችው) ፎሲት ገበያ ትባል ነበር፡፡ ከጊዜ በኋላ የፎሲት ገበያ ታጠፈችና በቋሪት ከተማ ዳቢ ላይ ቆመች፡፡ ከተማይቱም እስከተወሰነ ጊዜ ድረስ ዳቢ ስትባል ቆይታ አሁን ገበዘ ማርያም ተብላ ትጠራለች፡፡ ይህች ውብና ስትራቴጂያዊ ከተማ የተቆረቆረችው በ1955 ዓ.ም ላይ ነው፡፡ በከተማዋ ዙሪያ ዘብ የቆሙ ወታደሮች መስለው ተራራዎች ከብበዋታል፡፡ ከፊት ለፊት ታላቁ የጎምት ተራራ ይገኛል፡፡ ከጎምት ተራራ ቀጥሎ ሹል ተራራ የሚባለው ደረቱን ገልብጦ ቆሟል፡፡ ከሹል ተራራ ቀጥሎ ወስፌ ደንጋይ ተራራ ትገኛለች፡፡ ሌላው ቀስቀስ ተራራ ይሰኛል፡፡ ገበዘ ማርያም ልክ እንደ ዐድዋ የተራራ ሰልፈኛ ወታደር ይበዛባታል፡፡ ረድፉን ተከትሎ አዙሮ አምባ ተራራ፣ ዐመድ በር ታራራ፣ አዳማ ተራራ፣ አብርሃም ተራራ፣ ተራሮቹ በጣም የበዙ ናቸው፡፡ ቦታው ለሰማይ የቀረበ ስለሚመስልና ደጋም ስለሆነ፣ አየሩ በእጅጉ ቀዝቃዛና ነፋሻ ነው፡፡ ጫካ ይበዛዋል፡፡ የደጋ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ልዩ ልዩ ሰብል ይበቅልበታል፡፡ ፈረስ በብዛት ይረባበታል፡፡ ውሀው በጣም ይጣፍጣል፡፡ ከየ ተራሮቹ ሥር ዐራት አፍላጋት ይፈልቃሉ። እነርሱም ወደ ደቡብ አቅጣጫ የሚፈስሰው የብር ወንዝ፣ ወደ ሰሜን የሚወርደው ጡል ወንዝ፣ ወደ ምሥራቅ የሚዘልቀው የሺና ወንዝ፣ ወደ ምዕራብ የሚጓዘው የጀማ ወንዝ ናቸው፡፡ ሺገዝም በአካባቢው ውህጥ /የተዋጠ/ ሆኖ ይፈስሳል፡፡ ነጭ ውሃጎኖ ውሀ ሲዖሎ የተባሉ ወንዞችም በሺና ወንዝ በኩል ወርደው ከየቃ ወንዝ ጋር ይገናኛሉ። የቃም ሞጣ አካባቢ ከሚገኘው ዐቢያ ወንዝ ጋር ይቀላቀላል፡፡ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት አፍላጋት ኅብር እየሠሩ ከታላቁ ዐባይ ጋር ይቀላቀላሉ፡፡ የዐባይ ወንዝ መፍለቂያ የሆነው ሰከላም ከብር አዳማ በታች 20 ኪ.ሜ ላይ ይገኛል፡፡ በቋሪት ተራራ የተፈተነው ሙሽራ እንደገለጠልኝ፤ ቀደም ሲል በቋሪት ለሀገር ዋስና ጠበቃ፣ የተጣላን አስታራቂ፣ የተከበሩና የታፈሩ፣ የታወቁ የሀገር ሽማግሌዎች ይኖሩ ነበር፡፡ ለአብነት ያህል እነ ጎሹ ገሠሠ፣ እነ ብዙነህ ደስታ፣ አድገህ ንጉሤ(ግራዝማች)፣ ስንሻው ካሣ፣ ይመኔ መነሾና ከልካይ መነሾ፣ ነጋሽ መስፍንና አያልነህ መስፍን (ሁለቱም ግራዝማቾች)፣ ሺፈራው ፈንታ፣ ገላየ፣ አረጋ ተበጀ (ፊታውራሪ) እሸቴ አይቼህ … የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡ ቀደም ሲል በደርግ ዘመነ መንግሥት በቋሪት ሕዝብና በደርግ ባለሥልጣኖች መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር፡፡ የጠቡ መነሻ አብዮተኛና ፀረ አብዮተኛ የሚል ነው፡፡ ሁለት ተማሪዎች ከጂጋ ከተማ ተነሥተው በእግር ወደ ቋሪት ሲሄዱ በወቅቱ የደምስስ ጦር አዛዥ የጂጋም ወረዳ አስተዳዳሪ የነበረና ስሙን መግለጥ የማልፈልገው ሰው፣ ተማሪዎቹን የኢሕአፓ ወረቀት ልትበትኑ ነው ወደ ቋሪት የምትሄዱት ብሎ በመያዝ ይገድላቸዋል፡፡ የወቅቱን የቋሪት ወረዳ አስተዳዳሪ ቀኛዝማች ውበቴ ደስታንና የፖሊስ አዛዡን 10 ዓለቃ እምሬ ፈንታን ለመያዝ ፈልጎ በአስቸኳይ እንድትመጡ ብሎ ቢልክባቸው እምቢ ይላሉ፡፡ በዚህ ጊዜ “የውበቴንና የእምሬን ጭንቅላት ቆርጬ ባላመጣ እናቴ አልወለደችኝም” ብሎ የደምስስ ጦር አዛዥ ጂጋና ፍኖተ ሰላም እየረገጠ ይፎክራል፡፡ ያስፎክራል። በመኻሉ ደምሳሹ ታጋይ ጦሩን አክቶ ወደ ቋሪት እየመጣ ነው መባልን የሰማው የቋሪት ሕዝብ “ወንድሞቻችንን አሳልፈን እንደ ይሁዳ አንሰጥም” በሚል ቀድሞና ቁልቁል ወርዶ ዝንድብ ከተባለው ቦታ ይጠብቀዋል፡፡ እንደተገናኙ ደምሳሾቹ በአውቶማቲክ መሣሪያ በሕዝቡ ላይ ጥይት ያርከፈክፉበት ጀመር፡፡ ከላይ ከተራራው አክቶ የወረደው የገበሬ ጦር ዝንድብ ላይ ዘመናዊ መሣሪያ ከታጠቀው የደርግ ሠራዊት ጋር ጦርነት ገጥሞ የሚሞተው እየሞተ ግር ብሎ ግፋኑን ወደ ፊት በመሔድ የደምስስን ጦር አዛዥ ይማርከዋል፡፡ ከዚያም የቋሪት የገበሬ ጦር፣ ልብሱን አውልቆ በግራር ዛፍ ላይ ሰቅሎታል፡፡ የደርግ መንግሥትም አባሪ ተባባሪ ናቸው ያላቸውን የቋሪት ጀግኖች አድኖ በመያዝ ረሽኗቸዋል። በወቅቱ በነበረው ሽብር የተነሣ የደብረ ማርቆስ ከተማ ከፍኖተ ሰላም፣ ከጅጋ፣ ከደንበጫ በተፈናቀሉ ስደተኞች ቁጥር ተጥለቅልቃ ነበር። ስለቋሪት ሕዝብ ጀግንነት አስቀድሞ የማውቀው ብዙ ነገር ቢኖርም በሥራ አጋጣሚ ቋሪት በቅርቡ ሄጄ በነበረበት ጊዜ ከጀግንታቸው ባሻገር ዐራት ነገሮችን በፍጥነት ተረዳሁ፡፡ እነርሱም ትሕትናና እንግዳ አክባሪነት፣ ፉከራና ቀረርቶ ወዳድነት፣ የፍቅር ዘፈን ግጥም ደርዳሪነት ናቸው፡፡ ቋሪቶች እንግዳ ተቀባዮች ናቸው የምለውም ያለምክንያት አይደለም፡፡ ገበዘ ማርያም ከተማ እንደገባሁ ምሳ ለመብላት ወደ አንድ ሞቅ ደመቅ ወደ አለ ምግብ ቤት ዘለቅሁና ምሳየን በላሁ፣ ጠጣሁ፡፡ አጠገቤ ቁጭ ብለው ምሳ ሲመገቡ የነበሩ ወጣቶች ጠጉረ ልውጥ መሆኔን ተገንዝበው ከየት ለምን ዓላማ እንደመጣሁ ጠይቀውኝና ተዋውቀውኝ ስንጨዋወት ቆየን። በኋላ ለምግብ ገንዘብ ለመክፈል ስነሣ “ልጆቹ ከፍለውልዎ ሔደዋል” አሉኝ፡፡ በኋላ ስረዳ ልጆቹ የቋሪት ንግድ ባንክ ሠራተኞች እንደሆኑ አወቅሁ። ማታ ደግሞ በአጋጣሚ ከወረዳው ቤተክህነት አስተዳዳሪና ሠራተኞች ጋር መተዋወቄን ምክንያት አድርገው ራት ጋብዘው፣ ለአልጋም ከፍለውልኝ እንደሄዱ ተነገረኝ። በየ ሱቁ በሄድኩበት ሁሉ መስተንግዷቸው ይማርካል፡፡ በትራንስፖርት ረገድ በአካባቢው ትልቁ ችግር መኪና ነው፡፡ የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት መኪና መድቦልኝ ብር አዳማ ንኡስ ከተማ ድረስ ጋቢና በክብር አስቀምጦ ልዩ መስተንግዶ አድርጎልኛል። ከዚህም የተነሣ ለሁልጊዜም የሕዝቡ እንግዳ አክባሪነት፣ ፍቅሩና ትሕትናው ከልቤ ውስጥ ይኖራል፡፡ ቋሪት ጎበዘ ማርያም ከተማ ሲያስተጋቡ ስለሰማኋቸው የፉከራ የሽለላ፣ የዘፈን/የፍቅር ግጥሞች በጥቂቱ ለአንባቢዎቼ ለማስገንዘብ ከቀረርቶዎቹ እጀምራለሁ፡፡ “ቤቴ በረሀ ነው ጫካ ነው አገሬ፣ ማን ደጄን ረግጦት መቼ ተናግሬ፡፡ ቀን ያወጣል ብለው የዘሩት በቆሎ፡፡ ፍሬ ሳይሰጥ ቀረ ያለጊዜው በቅሎ፡፡ ገና ሳይታወቅ ክፉ ይሁን በጎ፡፡ እንዴት ሰው ይቆርጣል አንድ አንጀት ፈልጎ፡፡ ቡሬ አለ ጠመንጃ ሰከላ አለ ጥይት፡፡ ከተኮሰ አይስትም አነጣጥሮ ቋሪት፡፡ አትንኩኝ ማለቱ የእናት ያባቱ ነው፡፡ ምን ይገኝበታል ደሞ የቋሪት ሰው፡፡” ስለጎጃም ጀግኖች የሚከተሉት ዘፈኖች ይዘፈናሉ፡፡ “የተወለድኩብህ ቋሪት ደጋ ዳሞት፣ አርገኝ እንደበላይ ሰው ፈርቼ እንዳልሞት፡፡ አባቴ የሰጠኝ ሱሪ ከሚቀደድ፣ መታነቅ ይሻላል መሰቀል በገመድ፡፡ ስለቴ ቢሰምር ነግሬያለሁ ለዐባይ፣ ከማይሞቀው ኑሮ አርገኝ እንደ በላይ፡፡ ሺፈራውም ሞተ እጅጉም ቆሰለ፡፡ የበላይ በልጅጉ መሬት ወርዶ ዋለ፡፡ እምቢ አለ ጠመንጃው አልተኩስም አለ፡፡ በላይ በዐደባባይ ስለተሰቀለ፡፡” “የጎጃምን ሱሪ ሰፊ አበላሽቶበት፣ መንገደኛው ሁሉ ጉልበቱን አየበት ቋሪትንና ብር አዳማን የሚያናውጡ የፍቅር ግጥሞችም አሉ፡፡ ለአብነት ያህል ጥቂቶቹ ተጠቅሰዋል፡፡ “አዳማ ላይ ሆኘ ባስጠራሽ አቦላ፣ ዐባይ ከጠበሉ ሄድሽ አሉኝ ሰከላ፡፡ መቼ ትመጫለሽ መቼ ልጠብቅሽ፣ ዋሸራ ወጥቼ ቅኔ እንድዘርፍልሽ፡፡ ጎንጅነሽ ቆለላ ዋሸራ ማርያም፣ ወርደሽ እንገናኝ ኢየሱስ ገዳም፡፡ ነይ ከደጋ ዳሞት፣ ናፍቄሽ እንዳልሞት፡፡ ጨካኝ ናት እያሉ ሲሉ ሰማኋቸው፡፡ ካልነኳት አትነካም ብየ ነገርኳቸው፡፡ እንዲህ ብለሽ ብለሽ የመጣሽ እንደሆን፣ አገሩ ይሰብሰብ አልችልም ብቻየን፡፡ ድረሽ በማለዳ፣ ድረሽ ከብት ስንነዳ፡፡ ድረሽ በማለዳ ድረሽ፣ ከብቶቹን ይዘሽ፡፡ ድረሽ በማለዳ፣ የፍቅር እንግዳ፡፡ እጠብቅሻለሁ ቤቴን አሳምሬ፣ ሌሊቱ ሲነጋ ድረሽልኝ ፍቅሬ፣ እኔ አልተመቸኝም ጅጋ ነው አዳሬ፡፡ ከብት አሰማርቼ ከላይ ከተራራው፣ ከታች ሆነሽ ጥሪኝ ብቅ ብለሽ ከማማው፡፡ ያው ደበሎ ለባሽ እረኛ ነኝና፣ እጠብቅሻለሁ ደርሰሽ ጥሪኝና፡፡ ወይ ወርጀ ልምጣ ከብቶቹን ለቅቄ፣ አላማረብኝም ከወዳጅ ርቄ፡፡ ከማታው ወድጀ አንቺን ስል፣ አንቺን ስል፣ አስፈጀሁ የሰው እህል፡፡ ትመጫለሽ ብየ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ፣ ዓይኔ ሆነ ባዶ፡፡ እንዲያው ከፈረሱ ከለመድሺው በቅሎ፣ ወንድ እንዳይስቅብኝ በእኔ ግዳይ ጥሎ፡፡ እመጣለሁ ብለሽ ነግረሽኝ ነበረ፣ እናስ ምነው ጠፋሽ ቤቴ ክፍት አደረ፡፡ አንቺ የንጋት ወፍ የማለዳ እንግዳ፣ መቼ ብቅ ትያለሽ ባንቺ እኔ ስጎዳ፡፡ ቀኑ አልተመቸኝም ዐርባ ነው ሌሊቱ፣ እንቅልፍ ያልወሰደኝ ጥሎብኝ ነው ብርቱ፡፡ በዳር እንዳዋልሺው እንደመቀነትሽ፣ ጣል አርገሽ ነጠላ አርጊኝ በወገብሽ፡፡ ገና በልጅነት ስትግደረደሪ፣ መብላት ያለብሽን ሳትበይ እንዳታድሪ፡፡” ልጃገረዶች ደግሞ ቆንጆዎች፣ ረጃጅሞችና ወገበ ቀጭኖች ናቸው፡፡ ባለትዳር ያልሆነ ሰው በቀላሉ በቋሪት ልጃገረዶች የአነጋገር ለዛ፣ ፈገግታና ውበት ተማርኮ እዚው የመቅረት ዕድሉ የሰፋ ነው፡፡ ደግነቱ እኔ ባለትዳር መሆኔ ጠቀመኝ፡፡ በቋሪት ተራራ የተፈተነው ሙሽራም ከምሥራቁ የጎጃም ክፍል ወደ እኛው ምዕራብ ጎጃም ዞን መጥቶ ቋሪት የቀረው በአንዲቱ ወጣት ውበት ተማርኮና በፍቅርዋ ተነድፎ ነው፡፡ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በፊት የፍ/ቤት ጸሐፊ፣ በኋላ ዳኛ የነበረው አቶ ዋልታንጉሥ ጥበቡ ይባላል፡፡ ተፈቃሪዋ ደግሞ የያኔዋ ወጣት ጦቢያው አበሻ ትባላለች፡፡ በአቶ ዋልታንጉሥ ልብ ውስጥ ሁነኛ ስፍራ ስለአገኘች አቶ ዋልታንጉሥ ሽማግሌ ልኮ ቀን ቆርጦ ያገባታል፡፡ ጋብቻውን ምክንያት በማድረግም በሹል ደንጋይ አናት ላይ የምትኖረው የሙሽራዋ ታላቅ እህት ሙሽሮችን መልስ ይጠራሉ፡፡ ሙሽሮቹ ሚዜዎቻቸውን አስከትለው እስከ ተራራው ጥግ ድረስ በመከራ ይጓዛሉ፡፡ ከዚያ ሌሎች እንደምንም በደረት እየተሳቡ ከተራራው ሹል ድንጋይ አናት ላይ ሲደርሱ የያኔው የፍርድ ቤቱ ጸሐፊ ሙሽራው ዋልታ ከመንገድ ወደ ከተማው ይመለሳል፡፡ ሚዜዎቹ ሙሽራዋን ይዘው ወደ ድግሱ ቤት ሲያመሩ፣ የሙሽራዋ ታላቅ እህት ሙሽራውስ? ይላሉ፡፡ “ተራራውን ለመውጣት ስለአልቻለ ከመንገድ ተመልሷል” ይሏቿል፡፡ በዚህ ጊዜ የሙሽራዋ እህት “ሙሽራው ዳኛ በወሰካም ቢሆን ካልመጣ በምንም ታምር የጠላው ጋን አይከፈትም፣ የመሶቡ እንጀራም አይቀርብም” ይሏቸዋል፡፡ ከዚያ የፍርድ ቤቱ ጸሐፊ እስከ ተራራው ጥግ ድረስ በበቅሎ ከሄደ በኋላ፣ በጠንካራ ጎረምሶች በወሳንሳ (በቃሬዛ) ተይዞና ወደ ተራራው አናት ወጥቶ የመልሱን ድግስ ከበላ በኋላ፣ በወሰካ ተኝቶ ተራራውን ከወረደ በኋላ ወደ ቋሪት ገበዘ ማርያም ተመልሷል፡፡
==References==
==References==
{{Reflist}}
{{Reflist}}

Revision as of 09:05, 9 May 2021

Quarit
ቋሪት
Flag of Quarit
ZoneMirab Gojjam
RegionAmhara Region
Area
 • Total602.99 km2 (232.82 sq mi)
Population
 (2012 est.)
 • Total124,309 [1]

Quarit (Amharic: ቋሪት ) is one of the woredas in the Amhara Region of Ethiopia. Part of the Mirab Gojjam Zone, Quarit is bordered on the southwest by Jabi Tehnan, on the west by Sekela, on the north by Yilmana Densa, on the east by the Misraq Gojjam Zone, and on the southeast by Dega Damot. The major town in Quarit is Gebeze Mariam. Goncha woreda was separated from Quarit.

The highest point in this woreda and in the West Gojjam Zone is Mount Amedamit , a part of the Choqa Mountains, with an elevation of 3619 meters. Mount Adama, from which the river Birr one of the tributaries of Blue Nile river starts its flow is one of the highest picks in the woreda. It was at the foot of this mountain that the Battle of Amedamit was fought on 6 October 1620 between Ras Sela Kristos, half-brother of the Emperor Susenyos of Ethiopia, and a group of rebels who opposed Susenyos' Pro-Catholic beliefs. The rebels were crushed.[2]

Demographics

Based on the 2007 national census conducted by the Central Statistical Agency of Ethiopia (CSA), this woreda has a total population of 114,771, an increase of -16.49% over the 1994 census, of whom 56,767 are men and 58,004 women; 4,750 or 4.14% are urban inhabitants. With an area of 602.99 square kilometers, Quarit has a population density of 190.34, which is greater than the Zone average of 158.25 persons per square kilometer. A total of 25,402 households were counted in this woreda, resulting in an average of 4.52 persons to a household, and 24,927 housing units. The majority of the inhabitants practiced Ethiopian Orthodox Christianity, with 99.96% reporting that as their religion.[3]

The 1994 national census reported a total population for this woreda of 137,437 in 27,875 households, of whom 69,044 were men and 68,393 were women; 2,008 or 1.46% of its population were urban dwellers. The largest ethnic group reported in Quarit was the Amhara (99.95%). Amharic was spoken as a first language by 99.9%. The majority of the inhabitants practiced Ethiopian Orthodox Christianity, with 99.9% reporting that as their religion.[4]

Tourist attractions

  • Haregewoyin cave, which is over 10 kilometer in its distance and very attractive. Used by the local people as a shelter during the summer season.
  • Gragn Ahmed standing land stone
  • Ambaw washa

ታሪክ

  • ቋሪት በምዕራብ ጎጃም ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች አንደኛው ነው፡፡ ወደ ቋሪት ለመዝለቅ ሁለት መንገዶችን መጠቀም ግድ ይላል፡፡ ይኸውም በጂጋ ከተማ በኩል በመኪና ወደ ላይ 45 ኪሎ ሜትር በመጓዝ፣ ወደ ወረዳው ከተማ ገበዘ ማርያም ለመድረስ ይቻላል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በሞጣ ባሕርዳር መንገድ ከይልማና ዴንሳ ወረዳ ከተማ ከአዴት በመኪና ወይንም በእግር ተጉዞ ወደ ገበዘ ማርያም ለመግባት ይቻላል፡፡ በተለይ ግን ከአዴት እስከ ብር አዳማና ቋሪት ከተማ ወይም ከጅጋ እስከ ገበዘ ማርያም ያለው መንገድ በእጅጉ አስቸጋሪ ነው። በእነዚያ መንገዶች የሚጓዝ መንገደኛ መኪናው እየነጠረ፣ ወገቡ እየተሰበረ ለመሄድ ይገደዳል። መኪናም እንደ ልብ ስለማይገኝ ነጋዴዎች ሸቀጦቻቸውን ከቦታ ወደ ቦታ የሚያመላልሱትና የሚገበያዩት በአጋሰ5ስ ላይ በመጫን ነው፡፡ በቋሪት አካባቢ ወይበይ፣ ብር አዳማና ጨጎዴ ሐና የተባሉ ቦታዎችን ስም በተደጋጋሚ መስማት የተለመደ ነው፡፡ የቋሪት ከተማ ገበዘ ማርያም በሰንሰለታማ ተራራዎች ሥር ትገኛለች፡፡ ቀደም ሲል ከተማዋ ዳቢ ትባል ነበር፡፡ የቋሪት የመጀመሪያ ገበያ (እናንጊያ ሚካኤል አጠገብ የተመሠረተችው) ፎሲት ገበያ ትባል ነበር፡፡ ከጊዜ በኋላ የፎሲት ገበያ ታጠፈችና በቋሪት ከተማ ዳቢ ላይ ቆመች፡፡ ከተማይቱም እስከተወሰነ ጊዜ ድረስ ዳቢ ስትባል ቆይታ አሁን ገበዘ ማርያም ተብላ ትጠራለች፡፡ ይህች ውብና ስትራቴጂያዊ ከተማ የተቆረቆረችው በ1955 ዓ.ም ላይ ነው፡፡ በከተማዋ ዙሪያ ዘብ የቆሙ ወታደሮች መስለው ተራራዎች ከብበዋታል፡፡ ከፊት ለፊት ታላቁ የጎምት ተራራ ይገኛል፡፡ ከጎምት ተራራ ቀጥሎ ሹል ተራራ የሚባለው ደረቱን ገልብጦ ቆሟል፡፡ ከሹል ተራራ ቀጥሎ ወስፌ ደንጋይ ተራራ ትገኛለች፡፡ ሌላው ቀስቀስ ተራራ ይሰኛል፡፡ ገበዘ ማርያም ልክ እንደ ዐድዋ የተራራ ሰልፈኛ ወታደር ይበዛባታል፡፡ ረድፉን ተከትሎ አዙሮ አምባ ተራራ፣ ዐመድ በር ታራራ፣ አዳማ ተራራ፣ አብርሃም ተራራ፣ ተራሮቹ በጣም የበዙ ናቸው፡፡ ቦታው ለሰማይ የቀረበ ስለሚመስልና ደጋም ስለሆነ፣ አየሩ በእጅጉ ቀዝቃዛና ነፋሻ ነው፡፡ ጫካ ይበዛዋል፡፡ የደጋ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ልዩ ልዩ ሰብል ይበቅልበታል፡፡ ፈረስ በብዛት ይረባበታል፡፡ ውሀው በጣም ይጣፍጣል፡፡ ከየ ተራሮቹ ሥር ዐራት አፍላጋት ይፈልቃሉ። እነርሱም ወደ ደቡብ አቅጣጫ የሚፈስሰው የብር ወንዝ፣ ወደ ሰሜን የሚወርደው ጡል ወንዝ፣ ወደ ምሥራቅ የሚዘልቀው የሺና ወንዝ፣ ወደ ምዕራብ የሚጓዘው የጀማ ወንዝ ናቸው፡፡ ሺገዝም በአካባቢው ውህጥ /የተዋጠ/ ሆኖ ይፈስሳል፡፡ ነጭ ውሃጎኖ ውሀ ሲዖሎ የተባሉ ወንዞችም በሺና ወንዝ በኩል ወርደው ከየቃ ወንዝ ጋር ይገናኛሉ። የቃም ሞጣ አካባቢ ከሚገኘው ዐቢያ ወንዝ ጋር ይቀላቀላል፡፡ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት አፍላጋት ኅብር እየሠሩ ከታላቁ ዐባይ ጋር ይቀላቀላሉ፡፡ የዐባይ ወንዝ መፍለቂያ የሆነው ሰከላም ከብር አዳማ በታች 20 ኪ.ሜ ላይ ይገኛል፡፡ በቋሪት ተራራ የተፈተነው ሙሽራ እንደገለጠልኝ፤ ቀደም ሲል በቋሪት ለሀገር ዋስና ጠበቃ፣ የተጣላን አስታራቂ፣ የተከበሩና የታፈሩ፣ የታወቁ የሀገር ሽማግሌዎች ይኖሩ ነበር፡፡ ለአብነት ያህል እነ ጎሹ ገሠሠ፣ እነ ብዙነህ ደስታ፣ አድገህ ንጉሤ(ግራዝማች)፣ ስንሻው ካሣ፣ ይመኔ መነሾና ከልካይ መነሾ፣ ነጋሽ መስፍንና አያልነህ መስፍን (ሁለቱም ግራዝማቾች)፣ ሺፈራው ፈንታ፣ ገላየ፣ አረጋ ተበጀ (ፊታውራሪ) እሸቴ አይቼህ … የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡ ቀደም ሲል በደርግ ዘመነ መንግሥት በቋሪት ሕዝብና በደርግ ባለሥልጣኖች መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር፡፡ የጠቡ መነሻ አብዮተኛና ፀረ አብዮተኛ የሚል ነው፡፡ ሁለት ተማሪዎች ከጂጋ ከተማ ተነሥተው በእግር ወደ ቋሪት ሲሄዱ በወቅቱ የደምስስ ጦር አዛዥ የጂጋም ወረዳ አስተዳዳሪ የነበረና ስሙን መግለጥ የማልፈልገው ሰው፣ ተማሪዎቹን የኢሕአፓ ወረቀት ልትበትኑ ነው ወደ ቋሪት የምትሄዱት ብሎ በመያዝ ይገድላቸዋል፡፡ የወቅቱን የቋሪት ወረዳ አስተዳዳሪ ቀኛዝማች ውበቴ ደስታንና የፖሊስ አዛዡን 10 ዓለቃ እምሬ ፈንታን ለመያዝ ፈልጎ በአስቸኳይ እንድትመጡ ብሎ ቢልክባቸው እምቢ ይላሉ፡፡ በዚህ ጊዜ “የውበቴንና የእምሬን ጭንቅላት ቆርጬ ባላመጣ እናቴ አልወለደችኝም” ብሎ የደምስስ ጦር አዛዥ ጂጋና ፍኖተ ሰላም እየረገጠ ይፎክራል፡፡ ያስፎክራል። በመኻሉ ደምሳሹ ታጋይ ጦሩን አክቶ ወደ ቋሪት እየመጣ ነው መባልን የሰማው የቋሪት ሕዝብ “ወንድሞቻችንን አሳልፈን እንደ ይሁዳ አንሰጥም” በሚል ቀድሞና ቁልቁል ወርዶ ዝንድብ ከተባለው ቦታ ይጠብቀዋል፡፡ እንደተገናኙ ደምሳሾቹ በአውቶማቲክ መሣሪያ በሕዝቡ ላይ ጥይት ያርከፈክፉበት ጀመር፡፡ ከላይ ከተራራው አክቶ የወረደው የገበሬ ጦር ዝንድብ ላይ ዘመናዊ መሣሪያ ከታጠቀው የደርግ ሠራዊት ጋር ጦርነት ገጥሞ የሚሞተው እየሞተ ግር ብሎ ግፋኑን ወደ ፊት በመሔድ የደምስስን ጦር አዛዥ ይማርከዋል፡፡ ከዚያም የቋሪት የገበሬ ጦር፣ ልብሱን አውልቆ በግራር ዛፍ ላይ ሰቅሎታል፡፡ የደርግ መንግሥትም አባሪ ተባባሪ ናቸው ያላቸውን የቋሪት ጀግኖች አድኖ በመያዝ ረሽኗቸዋል። በወቅቱ በነበረው ሽብር የተነሣ የደብረ ማርቆስ ከተማ ከፍኖተ ሰላም፣ ከጅጋ፣ ከደንበጫ በተፈናቀሉ ስደተኞች ቁጥር ተጥለቅልቃ ነበር። ስለቋሪት ሕዝብ ጀግንነት አስቀድሞ የማውቀው ብዙ ነገር ቢኖርም በሥራ አጋጣሚ ቋሪት በቅርቡ ሄጄ በነበረበት ጊዜ ከጀግንታቸው ባሻገር ዐራት ነገሮችን በፍጥነት ተረዳሁ፡፡ እነርሱም ትሕትናና እንግዳ አክባሪነት፣ ፉከራና ቀረርቶ ወዳድነት፣ የፍቅር ዘፈን ግጥም ደርዳሪነት ናቸው፡፡ ቋሪቶች እንግዳ ተቀባዮች ናቸው የምለውም ያለምክንያት አይደለም፡፡ ገበዘ ማርያም ከተማ እንደገባሁ ምሳ ለመብላት ወደ አንድ ሞቅ ደመቅ ወደ አለ ምግብ ቤት ዘለቅሁና ምሳየን በላሁ፣ ጠጣሁ፡፡ አጠገቤ ቁጭ ብለው ምሳ ሲመገቡ የነበሩ ወጣቶች ጠጉረ ልውጥ መሆኔን ተገንዝበው ከየት ለምን ዓላማ እንደመጣሁ ጠይቀውኝና ተዋውቀውኝ ስንጨዋወት ቆየን። በኋላ ለምግብ ገንዘብ ለመክፈል ስነሣ “ልጆቹ ከፍለውልዎ ሔደዋል” አሉኝ፡፡ በኋላ ስረዳ ልጆቹ የቋሪት ንግድ ባንክ ሠራተኞች እንደሆኑ አወቅሁ። ማታ ደግሞ በአጋጣሚ ከወረዳው ቤተክህነት አስተዳዳሪና ሠራተኞች ጋር መተዋወቄን ምክንያት አድርገው ራት ጋብዘው፣ ለአልጋም ከፍለውልኝ እንደሄዱ ተነገረኝ። በየ ሱቁ በሄድኩበት ሁሉ መስተንግዷቸው ይማርካል፡፡ በትራንስፖርት ረገድ በአካባቢው ትልቁ ችግር መኪና ነው፡፡ የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት መኪና መድቦልኝ ብር አዳማ ንኡስ ከተማ ድረስ ጋቢና በክብር አስቀምጦ ልዩ መስተንግዶ አድርጎልኛል። ከዚህም የተነሣ ለሁልጊዜም የሕዝቡ እንግዳ አክባሪነት፣ ፍቅሩና ትሕትናው ከልቤ ውስጥ ይኖራል፡፡ ቋሪት ጎበዘ ማርያም ከተማ ሲያስተጋቡ ስለሰማኋቸው የፉከራ የሽለላ፣ የዘፈን/የፍቅር ግጥሞች በጥቂቱ ለአንባቢዎቼ ለማስገንዘብ ከቀረርቶዎቹ እጀምራለሁ፡፡ “ቤቴ በረሀ ነው ጫካ ነው አገሬ፣ ማን ደጄን ረግጦት መቼ ተናግሬ፡፡ ቀን ያወጣል ብለው የዘሩት በቆሎ፡፡ ፍሬ ሳይሰጥ ቀረ ያለጊዜው በቅሎ፡፡ ገና ሳይታወቅ ክፉ ይሁን በጎ፡፡ እንዴት ሰው ይቆርጣል አንድ አንጀት ፈልጎ፡፡ ቡሬ አለ ጠመንጃ ሰከላ አለ ጥይት፡፡ ከተኮሰ አይስትም አነጣጥሮ ቋሪት፡፡ አትንኩኝ ማለቱ የእናት ያባቱ ነው፡፡ ምን ይገኝበታል ደሞ የቋሪት ሰው፡፡” ስለጎጃም ጀግኖች የሚከተሉት ዘፈኖች ይዘፈናሉ፡፡ “የተወለድኩብህ ቋሪት ደጋ ዳሞት፣ አርገኝ እንደበላይ ሰው ፈርቼ እንዳልሞት፡፡ አባቴ የሰጠኝ ሱሪ ከሚቀደድ፣ መታነቅ ይሻላል መሰቀል በገመድ፡፡ ስለቴ ቢሰምር ነግሬያለሁ ለዐባይ፣ ከማይሞቀው ኑሮ አርገኝ እንደ በላይ፡፡ ሺፈራውም ሞተ እጅጉም ቆሰለ፡፡ የበላይ በልጅጉ መሬት ወርዶ ዋለ፡፡ እምቢ አለ ጠመንጃው አልተኩስም አለ፡፡ በላይ በዐደባባይ ስለተሰቀለ፡፡” “የጎጃምን ሱሪ ሰፊ አበላሽቶበት፣ መንገደኛው ሁሉ ጉልበቱን አየበት ቋሪትንና ብር አዳማን የሚያናውጡ የፍቅር ግጥሞችም አሉ፡፡ ለአብነት ያህል ጥቂቶቹ ተጠቅሰዋል፡፡ “አዳማ ላይ ሆኘ ባስጠራሽ አቦላ፣ ዐባይ ከጠበሉ ሄድሽ አሉኝ ሰከላ፡፡ መቼ ትመጫለሽ መቼ ልጠብቅሽ፣ ዋሸራ ወጥቼ ቅኔ እንድዘርፍልሽ፡፡ ጎንጅነሽ ቆለላ ዋሸራ ማርያም፣ ወርደሽ እንገናኝ ኢየሱስ ገዳም፡፡ ነይ ከደጋ ዳሞት፣ ናፍቄሽ እንዳልሞት፡፡ ጨካኝ ናት እያሉ ሲሉ ሰማኋቸው፡፡ ካልነኳት አትነካም ብየ ነገርኳቸው፡፡ እንዲህ ብለሽ ብለሽ የመጣሽ እንደሆን፣ አገሩ ይሰብሰብ አልችልም ብቻየን፡፡ ድረሽ በማለዳ፣ ድረሽ ከብት ስንነዳ፡፡ ድረሽ በማለዳ ድረሽ፣ ከብቶቹን ይዘሽ፡፡ ድረሽ በማለዳ፣ የፍቅር እንግዳ፡፡ እጠብቅሻለሁ ቤቴን አሳምሬ፣ ሌሊቱ ሲነጋ ድረሽልኝ ፍቅሬ፣ እኔ አልተመቸኝም ጅጋ ነው አዳሬ፡፡ ከብት አሰማርቼ ከላይ ከተራራው፣ ከታች ሆነሽ ጥሪኝ ብቅ ብለሽ ከማማው፡፡ ያው ደበሎ ለባሽ እረኛ ነኝና፣ እጠብቅሻለሁ ደርሰሽ ጥሪኝና፡፡ ወይ ወርጀ ልምጣ ከብቶቹን ለቅቄ፣ አላማረብኝም ከወዳጅ ርቄ፡፡ ከማታው ወድጀ አንቺን ስል፣ አንቺን ስል፣ አስፈጀሁ የሰው እህል፡፡ ትመጫለሽ ብየ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ፣ ዓይኔ ሆነ ባዶ፡፡ እንዲያው ከፈረሱ ከለመድሺው በቅሎ፣ ወንድ እንዳይስቅብኝ በእኔ ግዳይ ጥሎ፡፡ እመጣለሁ ብለሽ ነግረሽኝ ነበረ፣ እናስ ምነው ጠፋሽ ቤቴ ክፍት አደረ፡፡ አንቺ የንጋት ወፍ የማለዳ እንግዳ፣ መቼ ብቅ ትያለሽ ባንቺ እኔ ስጎዳ፡፡ ቀኑ አልተመቸኝም ዐርባ ነው ሌሊቱ፣ እንቅልፍ ያልወሰደኝ ጥሎብኝ ነው ብርቱ፡፡ በዳር እንዳዋልሺው እንደመቀነትሽ፣ ጣል አርገሽ ነጠላ አርጊኝ በወገብሽ፡፡ ገና በልጅነት ስትግደረደሪ፣ መብላት ያለብሽን ሳትበይ እንዳታድሪ፡፡” ልጃገረዶች ደግሞ ቆንጆዎች፣ ረጃጅሞችና ወገበ ቀጭኖች ናቸው፡፡ ባለትዳር ያልሆነ ሰው በቀላሉ በቋሪት ልጃገረዶች የአነጋገር ለዛ፣ ፈገግታና ውበት ተማርኮ እዚው የመቅረት ዕድሉ የሰፋ ነው፡፡ ደግነቱ እኔ ባለትዳር መሆኔ ጠቀመኝ፡፡ በቋሪት ተራራ የተፈተነው ሙሽራም ከምሥራቁ የጎጃም ክፍል ወደ እኛው ምዕራብ ጎጃም ዞን መጥቶ ቋሪት የቀረው በአንዲቱ ወጣት ውበት ተማርኮና በፍቅርዋ ተነድፎ ነው፡፡ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በፊት የፍ/ቤት ጸሐፊ፣ በኋላ ዳኛ የነበረው አቶ ዋልታንጉሥ ጥበቡ ይባላል፡፡ ተፈቃሪዋ ደግሞ የያኔዋ ወጣት ጦቢያው አበሻ ትባላለች፡፡ በአቶ ዋልታንጉሥ ልብ ውስጥ ሁነኛ ስፍራ ስለአገኘች አቶ ዋልታንጉሥ ሽማግሌ ልኮ ቀን ቆርጦ ያገባታል፡፡ ጋብቻውን ምክንያት በማድረግም በሹል ደንጋይ አናት ላይ የምትኖረው የሙሽራዋ ታላቅ እህት ሙሽሮችን መልስ ይጠራሉ፡፡ ሙሽሮቹ ሚዜዎቻቸውን አስከትለው እስከ ተራራው ጥግ ድረስ በመከራ ይጓዛሉ፡፡ ከዚያ ሌሎች እንደምንም በደረት እየተሳቡ ከተራራው ሹል ድንጋይ አናት ላይ ሲደርሱ የያኔው የፍርድ ቤቱ ጸሐፊ ሙሽራው ዋልታ ከመንገድ ወደ ከተማው ይመለሳል፡፡ ሚዜዎቹ ሙሽራዋን ይዘው ወደ ድግሱ ቤት ሲያመሩ፣ የሙሽራዋ ታላቅ እህት ሙሽራውስ? ይላሉ፡፡ “ተራራውን ለመውጣት ስለአልቻለ ከመንገድ ተመልሷል” ይሏቿል፡፡ በዚህ ጊዜ የሙሽራዋ እህት “ሙሽራው ዳኛ በወሰካም ቢሆን ካልመጣ በምንም ታምር የጠላው ጋን አይከፈትም፣ የመሶቡ እንጀራም አይቀርብም” ይሏቸዋል፡፡ ከዚያ የፍርድ ቤቱ ጸሐፊ እስከ ተራራው ጥግ ድረስ በበቅሎ ከሄደ በኋላ፣ በጠንካራ ጎረምሶች በወሳንሳ (በቃሬዛ) ተይዞና ወደ ተራራው አናት ወጥቶ የመልሱን ድግስ ከበላ በኋላ፣ በወሰካ ተኝቶ ተራራውን ከወረደ በኋላ ወደ ቋሪት ገበዘ ማርያም ተመልሷል፡፡

References

  1. ^ a b Geohive: Ethiopia Archived 2012-08-05 at the Wayback Machine
  2. ^ this battle is described in James Bruce 'Travels to Discover the Source of the Nile (1805 edition), vol. 3, pp. 353-355
  3. ^ Census 2007 Tables: Amhara Region Archived November 14, 2010, at the Wayback Machine, Tables 2.1, 2.4, 2.5, 3.1, 3.2 and 3.4.
  4. ^ 1994 Population and Housing Census of Ethiopia: Results for Amhara Region, Vol. 1, part 1 Archived November 15, 2010, at the Wayback Machine, Tables 2.1, 2.7, 2.10, 2.13, 2.17, Annex II.2 (accessed 9 April 2009)

11°10′N 37°15′E / 11.167°N 37.250°E / 11.167; 37.250 Template:Woredas of the Mirab Gojjam Zone

Leave a Reply